መዝሙር 271 የሱስ ክርስቶስ የኔ ወዳጅ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የሱስ ክርስቶስ የኔ ወዳጅ፥
እንደ እርሱ የለኝም።
ሌሎችም እንኳ ቢለዩኝ፥
እርሱ ግን አይተወኝም።
ማነው አሁን የሚለየኝ
ከየሱስ ክርስቶስ ፍቅር?
አንድነት ከእርሱ አለኝ፤
ማንም የማይወስድብኝ።
፪፡ እርሱ ሞተ ስለ እኔ፤
ማነው የሚፈርድብኝ?
አድኖኛል ከኵነኔ፤
ካምላክ ጋር አስታረቀኝ።
ማነው አሁን የሚወቅሰኝ?
እርሱ ራሱ መረጠኝ።
ማነው ከጁ የሚነጥቀኝ?
ጌታዬ ሲጠብቀኝ።
፫፡ ፍጹም ተስፋ አሁን አለኝ።
ሞትም ሆነ ሕይወትም
ከጌታዬ አይለየኝም።
ራብም ሆነ ጭንቀትም
ክብረት፥ ውርደት ወይም ኀዘን፥
ኃላፊ መጪም ቢሆን፥
ከዚህ ፍቅር አይለየኝም
ከየሱስ ካገኘሁት።