መዝሙር 242 ለየሱስ ስም ይሁን ስብሐት የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ለየሱስ ስም ይሁን ስብሐት
ኑ ለርሱ ስገዱለት
ምስጋናንም አቅርቡለት።
ኦ ይንገሥ ይንገሥ ይንገሥ
ንጉሠ ስብሐት።
፪፡ በደሙ የተገዛችሁ
ከሞትም የዳናችሁ
ስገዱለት ላነጻችሁ
ኦ ይንገሥ ይንገሥ ይንገሥ
ልዑል ጌታችን።
፫፡ ለርሱ ይሁን ምስጋናችን
ለልዑል አምላካችን
እናንግሠው በልባችን
ኦ ይንገሥ ይንገሥ ይንገሥ
መድኃኒታቸን።