Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 230 አምላኬ ምን ይሰጠኛል? የዘፈን ግጥሞች

መዝሙር 230 አምላኬ ምን ይሰጠኛል? የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009

 

(አንዱ ቡድን ሲጠይቅ ሁለተኛው ቡድን መልሱን ይዘምራል)
፩፡ አምላኬ ምን ይሰጠኛል?
– ይቅርታውን ይቅርታውን።
የኔ ልብ ገና ደንዝዞአል
– በርሱ እመን በርሱ እመን።
ረድኤቴ ከየት ይመጣል
– በደሙ ከገዛህ ጌታ።
፪፡ ኃጢአቴ ይሰማኛል
– አትፍራ ተሰቅሎልሃል።
ማነው ነጻ የሚያወጣኝ
– የሞተልህ የሞተልህ።
እንዴት ሰላም አገኛለሁ
– በቁስሉ ውሰጥ በችንካሩ።
፫፡ ዓለም ታስጨንቀኛለች
– አይዞህ ቤቱን ከፍቶልሃል
እረፍትም ትነሣኛለች
– የሱስ በእቅፉ ይይዝሃል።
ደስታውን ልቤ ይናፍቃል
– እመን ብቻ ይሰጥሃል።
፬፡ በጸጋው ያረካኛል ወይ?
– አትረፍርፎ ይሰጥሃል።
ለምን ቃሉ ይወቅሰኛል።
– እንዳትጠፋ ፈልጐሃል።
ይገስጸኛል በምክሩ?
– በፍቅሩ ይታደግሃል።

Exit mobile version