መዝሙር 213 መከራ የለም መጨነቅ የለም የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ መከራ የለም መጨነቅ የለም
ሁልጊዜ ክብር ይሆናል።
ማዘንም የለም ደስታ ብቻ ነው
በሰማይ ቤት ስንገናኝ።
ልቅሶ ልቅሶ የለም በዚያ
ጭንቀት ስቃይ ሁሉ ያልፋል።
ልቅሶ ልቅሶ የለም በዚያ
በሰማይ ቤት ስንገናኝ።
፪፡ አንድ ቀን በሰማይ መባከን የለም
እንዳለም የመከራ ኑሮ።
ሁሉ መልካም ነው ወዳጆች አሉ
ሁሉም አዲስ ነው እዚያ።
ልቅሶ ልቅሶ የለም . . .።
፫፡ ምስጋና ብቻ ምስጋና ብቻ
ፍጻሜ ከቶ የለውም።
ከጌታችን ጋር እንኖራለን
መከራችን ሁሉ ያልፋል።
ልቅሶ ልቅሶ የለም . . .።