መዝሙር 207 አምላክ ሆይ በቸርነትህ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አምላክ ሆይ በቸርነትህ
ሙሽሮችን ባርካቸው።
ኪዳናቸውንም አጽና
ቀድስ አንድነታቸውን።
በደስታ ሆነ በኅዘን
ስጣቸው ፍቅር ሰላም
ዘወትር ሁናቸው ተገን።
፪፡ ብፅዕናን አድላቸው
በፍርሃትህ አጽናቸው።
ፈተና ሲደርስባቸው
አንተ ረድኤት ሁናቸው።
ቢከብሩ ቢዋረዱ
ቢያገኙ ቢያጡ
በትዕግሥት ይኑሩ።
፫፡ በዓለም በሚቆዩበት
ባንተ ምክር ምራቸው።
እንዲረዳዱ በትዕግሥት
በጸጋህ ደግፋቸው።
ቸርነትህ አይለያቸው
ምሕረትህን ስጣቸው
እስኪፈጸም ዕድሜአቸው።
፬፡ ባንድነት በሚኖሩበት
ሁናቸው ኃይልና ብርታት።
ለምስጋናህ እንዲኖሩ
በመንፈስህ ይመሩ።
ረጅምም እድሜ ስጣቸው
እርጅና ሲጫናቸው
ልጆች ይደግፉአቸው።