መዝሙር 201 የልባችሁ ኃጢአት የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የልባችሁ ኃጢአት
እንደ ቅርምዝ ብትሆን፥
እንደ ደም ብትቀላ፥
እንደ ጥጥ ትነጣለች፤
ፈጽማ ትጠራለች
እንደ በረዶም።
እንደ ቅርምዝ ብትሆን፥
እንደ ደም ብትቀላ፥
ትነጣለች እንደ ጥጥ
እንደ በረዶም ደግሞ።
፪፡ አትርሳኝ ፈጣሪህ ነኝ
አሁንም እንተያይ።
እንደ ጭጋግ ይጠፋል
ኃጢአትህ በሙሉ።
እኔ ነኝ ሌላም የለም
የሚያድንህ።
ለእኔ ብትታዘዝ፥
በረከት ታገኛለህ፤
ከፍርድም ትድናለህ
ፈጽሞም ትነፃለህ።
፫፡ አትፍራ ትድናለህ፥
በስምህ ተጠርተሃል።
እጄንም ዘርግቻለሁ
ምርኵዝ ይሆንልህ ዝንድ።
ኃጢአትህን ያጠፋሁ
እኔ ብቻ ነኝ፤
እኔ ዋጅቼሃለሁ።
በስምህ ጠርቼሃለሁ።
ለዘላለም የኔ ነህ
ለዘላለም የኔ ነህ።