መዝሙር 20 ጌታ ከላይ በምድር ተገልጦአል የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ጌታ ከላይ በምድር ተገልጦአል
የአምላክ ልጅ በበረት ተወልዶአል።
የጥንቱ ትንቢትም ተፈጽሞአል
አምላክ ጐበኘን በታላቅ ፍቅሩ።
፪፡ ጽዮን ሆይ ብዙ ሺህ ዓመታት ቆየሽ
የመሢሕን መምጣት እየጠበቅሽ
አሁን ግን ተወልዶአል መድኃኒትሽ
ሰላም ሊሆንልሽ በልደቱ።
፫፡ መንጋቸውን የሚጠብቁ እረኞች
ሰሙ ሲዘምሩ የሰማይ ጭፍሮች።
ክብር ለአምላክ፥ ሰላምም ለሰዎች
ደኅንነት ሰጥቶአል ለሁሉ።