መዝሙር 193 አንተን የሱስ ሆይ እሻለሁ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አንተን የሱስ ሆይ እሻለሁ
እኔ ጥፋተኛ ነኝ።
ያለ አንተ እጠፋለሁ
ያለ አንተ የሞትሁ ነኝ።
ቅዱስ ክቡር ደምህ ብቻ
ሊጠራኝ ይችላል።
ያንተ ጽድቅ ያንተ ይቅርታ
እኔንም ያጸድቀኛል።
፪፡ አንተን የሱስ ሆይ እሻለሁ
እኔ ራሴ ዕውር ነኝ
ዘወትር እንከራተታለሁ
መንገዱን አላገኝም።
ና በእውነትህ ብርሃንም
እጄን ያዝና ምራኝ።
ባንተ ጽድቅና ሥልጣንም
ወደ መንግሥትህ አግባኝ።
፫፡ አንተን የሱስ ሆይ እሻለሁ
በዚህ ስደተኛ ነኝ።
ርስት በላይ ተቀብያለሁ
አንተ ራስህ ሰጠኸኝ።
ወደዚያ እጓዛለሁ፥
መንገዴም ጐርባጣ ነው።
የሱስ ሆይ አንተን እሻለሁ
ኃይልህ ብቻ ኃይሌ ነው።
፬፡ አንተን የሱስ ሆይ እሻለሁ
በደለኛን የሚችል።
አንድ ወዳጅ እፈልጋለሁ
ክፉውንም የማይጥል።
አንተም ሰርክ ትወደኛለህ
ከቶ አትጥለኝም።
ጉድለቴንም ታውቀዋለህ
ፍቅርህ ግን አይተወኝም።
፭፡ አንተን የሱስ ሆይ እሻለሁ
በፈቃድህም ምራኝ።
መንፈስህንም እሻለሁ
እርሱን የሱስ ሆይ ስጠኝ።
እርሱ ትልቅ ኃጢአቴን
ሁሉ ቀን ያሳስበኝ።
እርሱም የስርየት ብዛትን
ባንተ ቃል ያስተምረኝ።
፮፡ በምድራዊ ሕይወት ሳለሁ
ሲያልቅብኝም ቀኔ።
አንተን የሱስ ሆይ እሻለሁ።
እንድድን ከኩነኔ
አንድ እርምጃ ለመራመድ
ያለ አንተ አልችልም።
ካንተ ጋራ ግን ብዛመድ
አንዳች አይጐድልብኝም።
፯፡ አንተን የሱስ ሆይ እሻለሁ
አንተ ብቻ ሀብቴ ነህ።
አንተንም አንድ ቀን አያለሁ
በአብ ቀኝ ተቀምጠህ።
ወደ ሰማያዊ ቤቴ
አድነህ ስታደርሰኝ።
በደምህ ከተዋጁት ጋር
ለክብርህ ልዘምር ነኝ።