መዝሙር 178 የፈጠርከን አምላካችን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የፈጠርከን አምላካችን
ለኛም ትራራለህ።
ለሕፃናት አባት ሁናቸው፥
በርኅሩኅ እጅህ እቀፋቸው፥
አቅርበናቸዋል።
፪፡ የሱስ ክርስቶስ ከኃጢአታችን
ልታነፃን ወደሃል።
ይህንን ሕፃን ጠብቀው፥
በጥምቀት ልታነፃው፥
ወዳንተ ቀርቦአል።
፫፡ መንፈስ ቅዱስ መሪያችን ሆይ
የእውነት ቃልህን ግለጽልን።
ይህን ሕፃን አሳድገው፥
የአንተ እንዲሆን ጠብቀው፥
ወዳንተ ቀረቦአል።
፬፡ ቸሩ እግዚአብሔር ሆይ
በፍቅርህ ውስጥ እንዲኖር፥
ርስትህን እንድታወርሰው፥
እንማልድሃለን፥
ምስጋና እናቀርባለን።