መዝሙር 169 ቃልህን ኦ ቅዱስ ጌታ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ቃልህን ኦ ቅዱስ ጌታ
ልንሰማ ሰብስበን፥
በልባችን እንዳዝመራ፥
ሊዘንብልን ባርከን።
መንፈስ ቅዱስን ስጠን፥
ጸጋህንም ግለጥልን፥
ይርበናል መግበን
ጌታችን ሆይ ቃልህን።
ይርበናል መግበን
ጌታችን ሆይ ቃልህን።
፪፡ ቃልህንም ስትሰጠን
ልንቀበለው እርዳን፥
ብርሃንህንም አብራልን፥
መንገድህን አሳየን።
ካለማመን ጠብቀን፥
ከድንዛዜም አድነን፥
በጸጋህም አሳድገን፥
በሕያው ቃልህ ምራን።
፫፡ በከንቱ ዘመናችንን
እንዳናሳልፍ እርዳን፥
ጸጋህን እንዳናባክን፥
አምላክ ሆይ አሳስበን።
ቃልህንም ስትነግረን፥
እንድናስተውለው እርዳን፥
ልባችንንም አቅናልን፥
ልንታዘዝህ አብቃን
ልባችንንም አቅናልን፥
ልንታዘዝህ አብቃን።
