መዝሙር 142 ወዴት እሸሻለሁ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ወዴት እሸሻለሁ
ከአምለኬ ፊት?
ሰው የለም ከርሱ የሚሰወር።
የሚያስፈራራ የፍርድ ቀን ሲደርስ
እንዴትስ ልቁም ያለ ነውር?
እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ።
፪፡ ጭንቀት ሲይዘኝ
ሽቅብ ስመለከት
ከአርያም ይመጣል ረድኤቴ።
ቁልቁል ብመለከት ያሳፍረኛል
በምድር ተጻፈ ኃጢአቴ
እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ።
፫፡ የሱስ ሆይ በመስቀልህ
ስለ ፈሰሰው
ሰለ ደምህ ይቅርታ ስጠኝ
ለፍርድ ስትመጣ በምሕረትህ
ነፃ አድርገህ አቁመኝ
እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ።