መዝሙር 14 ደስታ ላለም የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ደስታ ላለም ጌታ መጥቷል፥
ምድር ተቀበይው፥
ልባችሁን አዘጋጁ።
ሰማይና ምድር
ባንድነት ዘምሩ፥
መዝሙር፥ መዝሙር፥ ለሕፃኑ።
፪፡ ደስታ ላለም አዳኝ ነግሦአል።
ሰዎች ዘምሩለት፥
ያለም ሜዳ ተራራውም
ደስታውን ይናገር።
ምድርም ትደሰት፥
ምድር፥ ምድርም፥ ትደሰት።
፫፡ ኃጢአት ይጥፋ ኀዘን ይራቅ፥
ምድርም ከሾህ ትረፍ።
በረከቱን ሊያፈስ መጥቷል፥
መርገምንም ሊሽር።
መርገምንም ሊሽር፥
መርገም መርገምንም ሊሽር።
፬፡ ያለም ገዢ ጻድቅ ፈራጅ፥
ሕዝቡን ሊያገለግል፥
የክብሩ ኃይል የጽድቁም ምንጭ፥
ፍቅር ከላይ ወርዷል።
ፍቅር ከላይ ወርዷል፥
ፍቅር ፍቅር ከላይ ወርዷል።