Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 139 እሻለሁ ጌታ የሱስን የዘፈን ግጥሞች

መዝሙር 139 እሻለሁ ጌታ የሱስን የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009

 

፩፡ እሻለሁ ጌታ የሱስን
ይቅር የሚል በደሌን
ጋሻ ይሆንልኛል
ከኃጢአት ይጠብቀኛል።
እርሱ ሕይወት ነው ለኔ
የሱስ ነው መድኃኒቴ።
፪፡ የሱስ አንተ ነህ ተስፋዬ
አዳኜና ሕይወቴ
ሁልጊዜ ነህ አምባዬ።
አንተ እምነት ካልሰጠኸኝ
አላገኘውም በራሴ
አንተ ነህ መድኃኒቴ።
፫፡ ስለዚህ ወዳንተ የሱስ፥
ጸጋህን ተማጥኜ፥
እመጣለሁ አምኜ።
ብርሃን ነህ ለሕይወቴ፥
ለተጨነቀ ልቤ
አንተ ነህ መድኃኒቴ።

Exit mobile version