መዝሙር 119 አምላክን በዕልልታ አመስግኑ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አምላክን በዕልልታ አመስግኑ
ወድሱት ሃሌ ሉያ
ልባችሁን ወደ ዙፋኑ አንሡ
ታላቁን ስሙን ወድ – ሱ።
በግርማው ኃይል ጠብቆናልና
ስብሐት ይሁን ክብር ምስጋና
በምድር ያላችሁ ሁሉ አምላክን አመስግኑ
በ – ዘመ – ናት ላ – ደረገው ሁ – ሉ
ጸንተን እናውለብልብ በደስታ ዓላማችንን
ለክብሩ እንዘምር እናድምቅ
ማኅሌታችንን።
በበገና በቀንደ መለከት እያስተጋባን
ምስጋና እናቅርብ ለታላቁ ንጉሥ።
፪፡ አመስግኑ ዘላለማዊውን ንጉሥ
ክብር ላምላክ በአርያም።
አመስግኑ ሰለ ታላቅ ፍቅሩ
ከመላእክቱ ጋር ወድሱት።
በጸጋው ለሚጎበኘን ጌታ
ምስጋና እናቅርብ በደስታ።
ከፍ ከፍም እናድርገው
በመዝሙር እንወድሰው።
ለሥሉሰ አምላክ ይሁን ምስጋና።
ጸንተን እናውለብልብ . . .።