Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 107 ቅዱሳን በጌታችን ፊት የዘፈን ግጥሞች

መዝሙር 107 ቅዱሳን በጌታችን ፊት የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009

 

፩፡ ቅዱሳን በጌታችን ፊት
ይቆማሉ፥
ይሰግዳሉ በሃይማኖት፥
በእርሱ ታምነው።
፪፡ ነጩን ልብሳቸውን ለብሰው
በእጃቸው
ዘንባባ ይዘው፥
ሰጡ ምስጋና እንዲህ ብለው
፫፡ በገናናነት ዙፋን ላይ
ለሚቀመጥ፥
ለአምላካችን በሰማይ፥
ክብር ምስገና እንስጥ።
፬፡ መላእክት በዙሪያው ቆመው
ሰገዱለት፥
ሽማግሎችም በዚያው
ምስጋና ሠዉለት።
፭፡ በግንባራቸው ወደቁ
ሰገዱለት፥
ለልዑል አምላክ ለበጉ
ምስጋና አቀረቡ።
፮፡ ግርማና ክብር ጥበብም
ለርሱ ይሁን፥
ምስጋናና ኃይል ችሎትም
ይሁንለት አሜን።

Exit mobile version