መዝሙር 100 መንፈስ ቅዱስ ሆይ ከእኔ ዘንድ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ መንፈስ ቅዱስ ሆይ፥ ከእኔ ዘንድ ሁን
እኔ ወዳንተ እንድጠጋ
አሙቀው የዛለ ፍቅሬን
መንፈስ ቅዱስ በልቤ ኑር።
፪፡ እርዳኝ እኔን ምስኪን ልጅህን
ፈተናን ሁሉ እንዳሸንፍ
በምሄድበት ቦታ ሁሉ
ጌታን ልከተል ሁልጊዜ።
፫፡ የሥጋን ምኞት አጥፋ ጌታ
በልቤ ይፍለቅ መንፈስ ቅዱስ
ትሑትና ታጋሽ ሁኜ
ከመስቀልህ በታች ልኑር።
፬፡ ጌታ ሆይ እርዳኝ በዚህ ቀን
ወዳባቴ ልይ በትጋት
ሁሉን ልታገሥ ኃይል ስጠኝ
አባቴ ዘንድ ሁሉም አለኝ።
፭፡ በዚህ ተማምኜ ልኑር
በአንተ ኃይል ተደግፌ
ድንቅ በሆነ ፍቅርህ ተስፋዬ
ልኑር ጌታ ሆይ በፊትህ።