Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 94 ከበደሌ ከኃጢአቴ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 94 ከበደሌ ከኃጢአቴ የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ ከበደሌ ከኃጢአቴ
ወዴት ልሽሽ ኦ አምላኬ?
በጣም እጨነቃለሁ
ሕግህን ሁሉ አፍርሼ
ከአንተ ርቄ ሸሽቼ
ፍርድህን እፈራለሁ።
ነፍሴን ኀዘን ደቆሰው
ልቤንም ጸጸት ሰበረው።
ጌታዬ ሆይ ራራልኝ
ምሕረት አድርግልኝ።
፪፡ አምላክ ሆይ ቃልህ ሕይወት ነው፤
ለነፍሴ በጣም ጣፋጭ ነው፤
ልቀበለውም እሻለሁ።
የሱስ ወዳለም መጥቶአል፤
ኃጢአቴን ደምስሶልኛል፤
እኔ በርሱ ድኛለሁ።
ወንበዴውን የተቀበለው፥
በገነትም ያሳረፈው፥
እኔን እንደሚቀበል፥
ቅዱስ ወንጌል ነግሮኛል።
፫፡ ይሱስ ክርስቶስ ይዳዊት ልጅ፥
ልቤን ከእጆቼ ጋራ
ወዳንተ አነሣለሁ።
እኔን የረከስሁ አጥራኝ፤
ከኃጢአት እድፍ አንፃኝ፤
በአንተ አምናለሁ።
እንደ ጠፋው በግ ነበርሁኝ፥
በአንተ ግን ተገኘሁኝ፤
አንተ የምትራራ
አኑረኝ ካንተ ጋራ።

Exit mobile version