Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 8 የሩሳሌም እልል በዪ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 8 የሩሳሌም እልል በዪ የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ የሩሳሌም እልል በዪ፤
የጽዮን ልጅም ዘምሪ።
ንጉሥሽ ይመጣልና
በምድር ሁሉ ሊገዛ።
፪፡ ጸጋና ጽድቅን ሊሰጠን
ከአባቱ ተላከልን።
ይሰጣልም ለሰው ሰላም
ከኃጢአት ሁሉ በማዳን።
፫፡ ምሥራች የነገረ መልአክ።
ተልኮልናል ከአምላክ።
በርሱ ያገኘነው ተስፋ
ይሰጠናል ታላቅ ደስታ።
፬፡ ስብሐት ለአምላክ በአርያም
በዓለምም ይሁን ሰላም።
ታላቅ ጸጋ የሰጠንን
በሙሉ ልብ እናመስግን።

Exit mobile version