Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 76 ለአምላካችን በሰማይ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ለአምላካችን በሰማይ፥
ይገባዋል ምስጋና፥
ስለ ጸጋው በእኛ ላይ፥
የሰጠው ለብፅዕና።
ለምድር ደስታና ሰላም፥
ሲሰጥ ይገባናል በጣም፥
ፈቃዱን ልንፈጽም።
፪፡ ኦ አባት ስላንተ ምሕረት፥
እናመሰግናለን።
አንተ በታላቅ ቸርነት፥
ጸጋን አወረድህልን።
ሥሉጥ እጅህ ሁሉን ይይዛል፥
ሥውር ኃጢአት ይታይሃል፥
ዳኝነትህ ይቀናል።
፫፡ የሱስ ክርስቶስ የልዑል ልጅ፥
ልታድነን የመጣህ፥
ከፍርድና ከሰይጣን እጅ፥
በሞት እኛን የዋጀህ፥
በትልቅ ምሕረትህ መጠን፥
ከመቅሠፍት ሞት ልታድነን፥
በአንተ ስንማጠን።
፬፡ በመንፈስህ ልባችንን፥
በቃልህ አጸናና።
ላንተ ምስጋና መቅደስህን፥
በየንፍሳችን ሥራ።
በመከራችን ደግፈን፥
አድስ ለጽድቅ ልባችንን፥
እምነትን ጨምርልን።