Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 7 በጸጋው እግዚአብሔር የዘፈን ግጥሞች
፩፡ በጸጋው እግዚአብሔር፥
የጠፋውን ሰው ሊያድን፥
አንድ ልጁን ወደዚች ምድር
ልኮአል ለሁላችን።
ዓለም በኃጢአት ብዛት
ፈጽሞ ወድቆ ሲኖር፥
መዳን ተስኖት፤
በየሱስ ክርስቶስ ሞት፥
ሆነለት ክብር፥ ሕይወት።
፪፡ ጌታችን የሱስ ክርስቶስ ሆይ፥
ሕይወትህን ለወጥህልን፤
በሞት ጥላ እንዳንቆይ፥
በመስቀል ላይ ሞትህልን።
ጌታ ሆይ ጸጋህ በዝቶአል፥
ኦ ያምላክ ልጅ ተመስገን፤
በምድር ሳለን፥
ምስጋናህ አንሶአል፥
በሰማይ ግን ይደምቃል።
፫፡ በክርስቶስ ግን ያላመነ
አሁን ተፈርዶበታል፥
አሁኑኑም ተኰነነ፤
በሥራውም ይጠፋል።
የወልድን ደም ያቃለለ
ብፅዕናን አያገኝም፤
ሕይወትም የለውም።
በወዲያኛው ዓለም፥
ይጠፋል ለዘላለም።