Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 49 ሕይወቴን ለወጥሁልህ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ሕይወቴን ለወጥሁልህ
ልገዛ ነፍስህን፥
ሰማይን ልከፍትልህ
ልሰጥህ ርስትህን።
ትድን ዘንድ ደሜ ፈሶአል
ምን መልሰህልኛል?
፪፡ ዙፋኔን ያባቴን ቤት
ትቼው ያንን ብርሃን፥
ባለም ጨለማና ሌት
በዚች ምድር ኅዘን
ስላንተ ነው ላንተ ብዬ
ምን ሆነ ዋጋዬ?
፫፡ ስላንተ ብፅዕና
እኔ ተሠቃየሁ፤
ስላንተም ብልጥግና
እኔ ደኸየሁ።
ስላንተ ሁሉንም ትቼ
ምን ሆነ ዋጋዬ?
፬፡ ከኃጢአት ከሞትም
ላድንህ መጣሁ፤
በልብህ ውስጥ ልኖርም
ደጅህን መታሁ።
ስጠኝ ልጄ ሆይ፡ ምኞቴን
ልብህን ደመወዜን።
