Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 36 መድኅኔ የሞተበትን የዘፈን ግጥሞች
፩፡ መድኅኔ የሞተበትን
ያንን መስቀል ስመለከት
እንቀዋለሁ ሕይወቴን
ይጠፋል የልቤ ትምክህት።
፪፡ ከቅዱስ መስቀልህ በቀር
ኦ ጌታዬ እንዳልመካ
ግለጥልኝ ያንተን ፍቅር
ያሳየኸውን በጎልጎታ።
፫፡ ልመልከት እጁንና እግሩን
በመስቀል ተቸንክሮአል
ተሸክሞልኝ ዕዳዬን
ክቡር ደሙን አፍስሶአል።
፬፡ ያለኝን ሁሉ ብሰጥህ
ፍጹም ያንስሃል ስጦታው
እነሆ አቀረብሁልህ
ነፍሴን ተቀበለኝ ይኸው።
