Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 340 የአምላካችንን ተአምራት የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 340 የአምላካችንን ተአምራት የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ የአምላካችንን ተአምራት
በኃይሉ የሚያደርገው፥
ለመላ ዓለም የሚገለጥ
ይህ ለኛ ደስታችን ነው።
የከይሲን ኃይል ያሸንፋል፤
የወደቁትን ያነሣል።
፪፡ የአምላክ ቃል በታላቅ ግርማ
በዓለም ውስጥ ያሸንፋል፤
ኃጢአተኛው እጁን ሰጥቶ
ምሕረቱን ይለምናል።
በየሱስ ደም ይታጠባል፤
ለአምላክም ክብር ይሰጣል።
፫፡ ወደ ዘላለም ብፅዕና
የሚጓዙት ብዙ ናቸው።
ከመላ ዓለም የሚመጡት
በክርስቶስ ተስፋ ያላቸው፥
ገና አሉ ይሚድኑ፥
በክርስቶስ የሚያምኑ።
፬፡ አሁን አዝመራውም እንደነጣ
በዓይናችሁ ተመልከቱ፤
ኃጢአተኞቹን ለመጥራት
ተነሥታችሁ አገልግሉ።
ንቁ ቁሙ በአንድነት፣
አውጁ የአምላክን ስርየት።

Exit mobile version