Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 338 ወንድሜ ሆይ ቶሎ ና የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ወንድሜ ሆይ ቶሎ ና።
ለምንስ ትዘገያለህ?
ጌታህም አንተን ይጠብቃል፤
ስፍራ ሊሰጥህ በርሱ ቤት፡፡
ለምን? ለምን?
ለምን ቶሎ አትመጣም
ለምን? ለምን?
ለምን ቶሎ አትመጣም?
፪፡ ወንድሜ ሆይ ቶሎ ዳን፤
በጌታ በየሱስ ጸጋ፡፡
ያለርሱ መድኃኒት የለህም
ፍፁሙም መንገድ እርሱ ነው፡፡
ለምን?. . .።
፫፡ ወንድሜ ሆይ አትቆይ፤
የርሱን ደኀንነት ተቀበል፡፡
ወደ ጌታህም እይ በእምነት፥
በደልህን ይቅር ይላል፡፡
ለምን?…፡፡
፬፡ ወንድሜ ሆይ አትቆይ፤
የመከሩ ጊዜ ያልፋል፡፡
ከመከራና ከድካምም
እርሱ ጌታ ያድንሃል፡፡
ለምን?…፡፡
