Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 335 ክርስቲያኖች ሆይ እንነሣ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ክርስቲያኖች ሆይ እንነሣ
እንገሥግስ በእልልታ
የሱስ ነው ከኛ ጋራ።
መስቀሉንም አንሸከም
ለመከተል ብንደክም፥
ሳይረዳን አይተወንም።
በቅን መንገድ ይመራናል
ከጒዳት ይጠብቀናል።
፪፡ የሱስ ገባ በጀግንነት
ጦር ወደ ተፋፋመበት
እንከተል በድፍረት።
ለጌታ ሰንደቅ ዓላማ
ተንቀን ብንታይ እንኳ
ከእውነት አንዛባ።
ይፈጸም የንጉሥ ተስፋ
ክብሩም በኛ ይንሰራፋ።
፫፡ አርበኞች ሁነን በፍጥነት
ብንዋጋ ሊመሠረት
ባለሙ ቅዱስ እውነት።
የሐሰት ምሽግ ይፈርሳል
ክፋት፥ ኃጢአት ድል ይሆናል
የሱስ ብቻ ይነግሣል።
ምሕረቱ በሚታይበት
ይሰፋል የወንጌል ትምህርት።
፬፡ ድንቅ፥ ኃያል አምላክ ነው ስሙ
የተሣለ ሰይፍ ነው ቃሉ
ታጠቀ በእውነቱ፥
በሚገባ ድል ይነሣል፥
ሁከት በሰላም ይተካል
ሰው ከጥፋት ይድናል።
የሚሠቃይ በባርነት፥
በርሱ ያገኛል አርነት።
፭፡ አባቶች እምነት ያዩት
ጻድቃን የተነበዩለት
ሰው ሆኖ ተወለደ
ሕዝቡ እየቀለዱበት
የሞተው በመስቀል እንጨት
በግርማው ይገለጣል
በመስቀሉ ላላፈሩ
ያካፍላል ከክብረቱ።
፮፡ ለግዛቱ እንሰለፍ
በሥራችን አንስነፍ፤
ቀን በከንቱ እናሳልፍ
ብርሃን በማይጠፋበት
በሰማይ በሚሰጠን ቤት
እናገኛለን ዕረፍት።
ከዚህ ምድር ስንሻገር
እልል እያልን እንዘምር።