Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 332 የጸድቅ ጸሐይ አሁን ወጣ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የጸድቅ ፀሐይ አሁን ወጣ፥
ብርሃኑ ድል ይነሣል።
ሕዝቦች ወንጌልን ሲሰሙ፥
የሱስን ያመልካሉ።
፪፡ የአምላካቸን ግርማ
በምድራችን ላይ በራ፤
ሌሊት አልፎ ቀን ሲተካ፥
እናመስግን በደስታ።
፫፡ እግዚአብሔር ያጸናል
በሰጠን የተስፋ ቃል፤
ምሕረቱንም ይሰጠናል፥
ሁልጊዜ ይረዳናል።
፬፡ ክርስቶስ ቶሎ ይመለሳል፥
ሕዝቡን ይሰበስባል
አሕዛብንም ይጠራል፥
ከብፅዕናው ይሰጣል።
፭፡ ቆነጃጅት ይወጣሉ
ንጉሡን ሊቀበሉ፤
ለጌታ ይዘምራሉ
ምስጋም ያቀርባሉ።
፮፡ እናንተ ሕዝቦች ተመልከቱ
ያምላክ ልጆች ሲመጡ፥
ፍጹም ነጭ የሐር ልብስ ለብሰው
ወደ ሰርጉ ሲገቡ።
፯፡ ባለም ይታወጅ ወንጌሉ
ይድረስ ለሰዎች ሁሉ።
ፍቅሩን ስለ ገለጠልን
ለዘላለም ይመስገን።