Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 318 ስንጓዝ በደረቅ አገር የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 318 ስንጓዝ በደረቅ አገር የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ ስንጓዝ በደረቅ አገር
ከዚህ ከሚጠፋ ዓለም፤
በዝማሬ እንሻገር
ወደ አዲስ የሩሳሌም።
እንደ ባሕር ሞገድ ጩኸት
በሰማያት መዝሙሩ ይደምቃል፤
ኃይል ምስጋና ክብር ስግደት
ላምላክ በግ ይገባዋል።
፪፡ በዚህ ታች ለስደተኞች
ኅዘን መከራ ይበዛል
ግን ለጽዮን መንገደኞች
አክሊል ተዘጋጅቶአል
እንደ ባሕር . . .።
፫፡ እስራኤል በባቤል ወንዞች
እያለቀሱ ሲኖሩ፤
የየሩሳሌምን ደጆች
ሁልጊዜ አስታወሱ።
እንደ ባሕር . . .።
፬፡ የሰማይ ወራሾች ሁሉ
በዚህ ታች እንዳትቀሩ፤
ባምላክ ኃይል ፣ በቅዱስ ቃሉ
በየቀኑ ተመሩ።
እንደ ባሕር . . .።

Exit mobile version