Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 309 የከበረ ቤቴ በሰማይ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 309 የከበረ ቤቴ በሰማይ የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ የከበረ ቤቴ በሰማይ፤
ማን ይተርካል መድመቅዋን?
የተመረጡት እንደ ፀሐይ
ይደምቃሉ በአምላክ ብርሃን።
በሰማይ፥ በሰማይ
የከበረ ቤት በላይ፤
በሰማይ፥ በሰማይ
ኦ ብፁዕ ሰላም በሰማይ።
፪፡ እንዴት ያለ ግሩም ፍሥሐ
ጉዞአቸውን የጨረስዋት፥
የማይተረክ ሰላምና ደስታ
ያገኛሉ በፍቅሩ ብዛት።
በሰማይ . . .።
፫፡ መድኃኒቴ አለ በዚያ
ዘመዶቼም ይጠብቁኛል።
የዚህን ምድር ኀዘን ልርሳው፤
ደስ ይበለኝ ከብፁዓን ጋር።
በሰማይ . . .።
፬፡ ቶሎ ወደዚያ ልግባ።
የንግድነቴ ዘመን ሲያልፍ፥
በዙፋኑ አንፃር በእልልታ፥
ከወዳጆቼ ጋር ልረፍ።
በሰማይ . . .።

Exit mobile version