Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 306 ሁሉም አለኝ፤ ሰላም አለኝ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 306 ሁሉም አለኝ፤ ሰላም አለኝ የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ ሁሉም አለኝ፤ ሰላም አለኝ፤
ሰላም አለኝ በልቤ በልቤ፥
ቅዱስ ቃሉን አንብቤ፥
ደኅንነት አግኝቻለሁ፤
ስሞት ወደ ጌታ እሄዳለሁ።
፪፡ በየሱስ ደም፥ በየሱስ ደም
ታጠበልኝ ኃጢአቴ፥ ኃጢአቴ፥
ተለወጠ ሕየወቴ፥
በወንጌል እጸናለሁ፤
ስሞት ወደ ጌታ እሄዳለሁ።
፫፡ እረፍት አለኝ፥ እረፍት አለኝ፥
እረፍት አለኝ በየሱስ፥ በየሱስ፥
የማይጠፋ ደስታ፥
የማይናወጥ ተስፋ፥
በሕይወቴ በጣም ተስፋፋ።
፬፡ ተለወጥኩኝ፥ ተለወጥኩኝ፥
ተለወጥኩኝ በየሱስ፥ በየሱስ፥
አዲስ ፍጥረት ሁኛለሁ፥
መንፈሱን አግኝቻለሁ፤
ስሞት ወደ ጌታ እሄዳለሁ።
፭፡ ኀዘን የለም፥ ጭንቀት የለም፥
ፍርሃት ጠፍቶአል ከልቤ፥ ከልቤ፥
መንፈሱ ያጽናናኛል፥
በደስታ ሞልቶልኛል፤
ጌታ ዞትር ይጠብቀኛል።
፮፡ ላመስግነው፥ ላመስግነው፥
ላመስግነው ጌታዬን፥ ጌታዬን፥
በመስቀል ተሠቃይቶ
ከፈለልኝ ዕዳዬን፤
ክብር፥ ክብር፥ ለስሙ ይሁን።

Exit mobile version