Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 297 አልጨነቅም ለመከራ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 297 አልጨነቅም ለመከራ የዘፈን ግጥሞች

 

አልጨነቅም ለመከራ
አምላክ ካለ ከእኔ ጋራ
አልጨነቅም ለመከራ
አምላክ ካለ ከእኔ ጋራ
፩፡ በሰጠኝ ተስፋ እጸናለሁ
በኢየሱስ ስም አምኛለሁ።
ከብስጭት እንድትድኑ
ሁላችሁም በእርሱ እመኑ።
ከብስጭት እንድትድኑ
ሁላችሁም በእርሱ እመኑ።
አልጨነቅም . . .።
፪፡ አትጨነቁ ለዚህ ዓለም
ከኢየሱስ የሚበልጥ የለም።
እናቶቼ አባቶቼ
አትታለሉ ዘመዶቼ
እህቶቼ ወንድሞቼ
አትዘንጉ ወገኖቼ።
አልጨነቅም . . .።
፫፡ ዓለም ያልፋል ሀብትም ሁሉ
የሚወዱን ይለያሉ።
ሞት ቢመጣ ጣር ሲከበን
ያኔ የለም የሚያድነን።
ሞት ቢመጣ ጣር ሲከበን
ያኔ የለም የሚያድነን።
አልጨነቅም . . .።
፬፡ ያታለሉን ነገሮች ሁሉ
ከፊታችን ይሸሻሉ።
የማይለይ የማይጠፋ
ኢየሱስ ነው ቋሚ ተስፋ።
የማይለይ የማይጠፋ
ኢየሱስ ነው ቋሚ ተስፋ።
አልጨነቅም . . .።
፭፡ ሁላችሁም ብልህ ሁኑ
በየሱስ አሁን እመኑ።
ተናዘዙ ለፈጣሪ
እርኅሩህ ነው ቸር መሐሪ።
ተናዘዙ ለፈጣሪ
እርኅሩህ ነው ቸር መሐሪ።
አልጨነቅም . . .።

Exit mobile version