Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 296 ደስ ይበለኝ ኀዘን ይራቅልኝ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 296 ደስ ይበለኝ ኀዘን ይራቅልኝ የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ ደስ ይበለኝ ኀዘን ይራቅልኝ፤
እግዚአብሔር ይወደኛል።
አምላካችን አባት ከሆነልኝ፤
ስለ ልጁ እርሱ ያስባል።
በየደቂቃው የደረሰኝን፥
አባቴ በፍቅሩ ልኮታል።
ለየቀኑም የሚጠቅመኝን
ደስታም፥ ኃዘንም ያካፍላል።
፪፡ ጩኸቴን ለመስማት አይሰለችም፤
ሸክሜንም ያነሣልኛል።
በድካሜ ከኔ ዘንድ አይለይም
ስሙም መካር ኃያል ይባላል።
ክቡር ገንዘቡ እንዳይጠፋበት፥
እርሱ ራሱ ይጠነቀቃል፤
እንደ ቀኑም ኃይሉ ሊሆንለት
ልጁን ጸጋው ያበረታዋል።
፫፡ አምላኬ እንዲህ ስታስብልኝ፥
እኔም ሐሳቤን ልተው እርዳኝ።
እምነቴን ከቃልህ ጨምርልኝ
በዚህም ወዳገሬ ምራኝ።
ደስ ሲለኝ ስጨነቅም በኀዘን፥
አንተ ሁሉን እንደ ሰጠኸኝ፥
ተስፋህን ተቀብዬ ለማመን
ጌታ ሆይ አንተ አስተምረኝ።

Exit mobile version