Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 290 ተስፋ የሰጠኝ ሕይወትም የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ተስፋ የሰጠኝ ሕይወትም
አንድ ስም ተገለጠ፤
ከምድር ከሰማያትም
ያ ድንቅ ስም በለጠ።
፪፡ ያ ቅዱስ ስም ነው አምባዬ
ረጅዬም በጭንቀት፤
በኃዘኔ ነው ደስታዬ፣
በችግሬም ሀብቴ።
፫፡ ያ ስም ስላንድ ርኅሩኅ ወዳጅ
ይተርክልኛል፤
ወዳጄም የሰማይን ደጅ
ለኔ ከፍቶልኛል።
፬፡ አባቴም እንዲቀበለኝ
ያ ስም ያስታውቃል፤
አንድ ብፁእ ወደብ እንዲገኝ
ያ ቅዱስ ስም ይላል።
፭፡ ስለሚረዳኝ ምሕረት
ያ ስም ይናገራል፤
ስጨነቅ ኃይልና ረድኤት
ዘወትር ይሰጠኛል።
፮፡ እንደኔም የተፈተነ
የሚራራልኝም፤
መድኅን እንደ ተሰጠነ
ይተርካል ያ ስም።
፯፡ ያ ብፁዕ ስምም ኢየሱስ ነው፤
እርሱ ነው ተስፋዬ።
ዕረፍቴና ሰላሜ ነው፤
በርሱም ነው ደስታዬ።
፰፡ ምድራዊ አፍ ያን ቅዱስ ስም
ሊያመሰግነው
አይበቃም እንጂ በአርያም
የብፁዓን መዝሙር ነው።
፱፡ ግን በዚያ ምድር በረሀ
ስሄድ ወዳገሬ፥
ያ ስም ነው የኔ ፍስሐ
ያ ስም ነው መዝሙሬ።
፲: አንድ ቀንም ወደ አገሬ
የሱስ ሲያደርሰኝ
አዲሱን መዝሙር ዘምሬ
ያን ስም ልወድስ ነው።