Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 271 አምላካችንን እናመስግን የዘፈን ግጥሞች
፩፡ አምላካችንን እናመስግን
ከዘላለም የነበረውን።
ልኮልናልና ታላቁን መድኀን
ከኃጢአታችን ያነፃንን።
እንገስግስ ታጥቀን
እንገስግስ ታጥቀን
የሃይማኖትን ዘውድ ተቀዳጅተን
የመንፈስንም ሰይፍ ጨብጠን።
፪፡ የሃይማኖት ጋሻ መክተን
የሰላምን ጫማ አድርገን።
የአምላክን የጽድቅ ጥሩር ለብሰን
በእውነት ሰቅ ወገባችንን ታጥቀን።
እንገስግስ ታጥቀን
እንገስግስ ታጥቀን
እንደ አምላካችን ቃል ጽድቁን ለብሰን
የመንፈስን ጫማ አድርገን።
፫፡ ምን ይዘን እንሂድ ለየሱስ
ስንደክም ቤታችን እንዳይፈርስ።
ለኛ ሲል ተዋርዶ እስከዚህ ድረስ
ደሙን እንደ ውኃ ሲያፈስ።
እንገስግስ ታጥቀን
እንገስግስ ታጥቀን
የሃይማኖትን ዘውድ ተቀዳጅተን
የመንፈስንም ሰይፍ ጨብጠን።