Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 259 ወዳምላክ ልብ የሚያደርስ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ወዳምላክ ልብ የሚያደርስ
አንድ ቅዱስ ደጅ አውቃለሁ፤
ከዚያም ደጅ ብርሃን ሲሠርፅ
መድኃኒቴን አያለሁ።
እንዴት ይገርማል አምላኬ፥
ያ ደጅ ተከፈተ ለኔ፥
ለኔ፥ ለኔ፥
ተከፈተ ለኔ።
፪፡ ያ ደጅ ለማንም አይዘጋም
ሊገቡ ለሚወዱ፤
ለጌታ ሆነ ለሎሌ
ለተጨነቀ ሁሉ።
እንዴት . . .።
፫፡ ስለዚህ ሂድ ወደዚህ ደጅ
በዚህ ግባ ሳይዘጋ፤
ዘውድ ለመቀበል ተዘጋጅ
በአምላካችን ጸጋ።
እንዴት . . .።
፬፡ አንድ ቀን ወደ ሰማይ ስንደርስ፥
ከመስቀል ስንፈታ፥
የሕይወት አክሊል ስንጭን፥
የሱስን ልናከብር።
እንዴት . . .።