Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 248 ዳግም ያልተወለደ ላዲስ ሕይወት የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 248 ዳግም ያልተወለደ ላዲስ ሕይወት የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ ዳግም ያልተወለደ ላዲስ ሕይወት
ያምላክን መንግሥት አያይም
ክርስቶስን ያልያዘ በልብ ሃይማኖት
ወደ ሰማይም አይገባም።
ደጁ ጠባብ ነው ተጋደል ለመግባት
ቀንም አጭር ነች እንዳታባክናት።
ልትጥር ያስፈልግሃል በፍርሃት
እንዳይቀርብህ ብፅዕናው።
፪፡ ሰምተህ ከመዳን ይከለክልሃል
ሰይጣን ያ ክፉ ጠላትህ
ባለም ደስታ ሁሉ ያታልልሃል
እንዳትድን ከጥፋትህ።
ምክሩን አትስማ ፍራው ወዳጄ ሆይ
ካለም ተንኰል ራቅ በዚያ አትቆይ
ንስሐ ለመግባትም አትዘግይ
የሱስ በፍቅር ሲጠራህ።
፫፡ በሰማይ ለጻርህ ለትግልህም
ምን ያህል ውሮታ አለህ?
ወዲያም ከደረስህ አይጸጽትህም
አክሊልህን ታገኛለህ።
ስለዚህ ተነሥ አሁኑ ተዘጋጅ
ጌታ ሳይመለስ የዓለሙ ፈራጅ
የሰርግ ልብስ ያልለበሰ በሰማይ ደጅ
እስከ ዘላለም አይገባም።
፬፡ እውነተኛ እምነት በልብህ ባይገኝ
ወደ ሰማይ አትደርስም
የክርስቶስን ጽድቅ ልትለብስ ባትመኝ
ሕይወትንም አትወርስም።
የምትድነው በእምነት ብቻ ነው
የክርስቶስን ጽድቅ አሁን ተቀበለው
የሱስም በፍቅር ሲጠራህ ስማው
እርሱን የሰማ ይድናል።
፭፡ የሕይወትን ዘውድ እንዲያገኝ በእምነት
ዓለሙ ሁሉ ተጠራ
ላንተም ዘውድ ተዋጀ በኢየሱስ ሞት
ለአንተ በፍቅሩ ራራ።
ታላቁ ጌታ እጅግ ያዝንልሃል
እጆቹን በፍቅር ዘርግቶልሃል
ከእንቅልፍህም ይቀሰቅስሃል
ብፁዕ ነህ ብትነቃለት።

Exit mobile version