Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 246 መንገዴ ሲጨልምብኝ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 246 መንገዴ ሲጨልምብኝ የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ መንገዴ ሲጨለምብኝ
ጌታዬ ሆይ ጠብቀኝ፤
ታውቃለህና አምላኬ
የማልችል ደካማ ነኝ።
መንገድ በሆንከው በአንተ
ልራመድ ኢየሱሴ፤
ወደ ተዋበው መንግሥትህ
እንድታመራ ነፍሴ።
፪፡ ያ ዲያብሎስ ይፍልጋል
በወጥመዱ ሊያጠምደኝ፤
በእርሱ መንገድ እንዳልሄድ
ጌታዬ ሆይ ጠብቀኝ።
የዓለም ፈተና ደግሞ እኔን
ሊያሠቃየኝ ፈልጓልና፥
የሱስ ሆይ፥
የኔን እጅ ይዘህ አውጣኝ።
፬፡ እኔ አፈር ነኝና ወዳፈር የምመለስ፥
አንተ ግን ሕያው አምላክ
ጠብቅልኝ የኔን ነፍስ።
ከእንግዲህ ወዲህ እጄን ያዝ፤
ሞት እኔን እንዳይገዛኝ
አምላኬ ሆይ እራራልኝ፤
ከሥቃይም አድነኝ።

Exit mobile version