Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 236 ብሩህ ፀሐይ ወጥቶአል የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ብሩህ ፀሐይ ወጥቶአል
ተመስገን አምላኬ
ባዲስ ተስፋ ባዲስ ኃይል
ልስገድ ተንበርክኬ፡፡
፪፡ ለበጎዎች ለክፎችም
ፀሐይህ ያበራል
እንዳንተ ርኅሩኅ የዋህም
መሆን ይገባኛል፡፡
፫፡ በዚህም ቀን ፈቃድህን
እንድፈጽም እርዳኝ
አሳስበኝም ሕግህን
በቃልህም ምራኝ፡፡
፬፡ አምላክ ሆይ ወዳንተ ስሸሽ
እኔን ተቀበለኝ
ሌሊት ሲነጋ ቀን ሲመሽ
ባባት ፍቅር እየኝ፡፡