Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 233 የሱስ እረኛዬ የሚመራኝ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የሱስ እረኛዬ የሚመራኝ
በሕይወት ጐዳና የሚወስደኝ።
እርሱን አገኘሁት የማይተወኝ።
ጓደኛ ወዳጅ ዘመድ ሲጠላኝ።
በመስቀል ላይ ተሠቃይቶ
የሞተልኝ የሱሴ፥
በፍቅሩ ይመራኛል፥
ይረዳኛል ሁልጊዜ።
በመስቀል ላይ ተሠቃይቶ
የሞተልኝ የሱሴ፥
በፍቅሩ ይመራኛል፥
ይረዳኛል ሁልጊዜ።
፪፡ የማልረባም ብሆን የማልችልም፥
በድካሜ ብዛት አይተወኝም።
ወደኔ ኑ ይላል ደካሞችን
እኔም በተስፋው ተጠጋሁ አሱን።
በመስቀል . . .።
፫፡ ሸክም ሲከብድብኝ ይወስድልኛል
ችግሬንም ያስወግድልኛል።
ፈተናም ሲመጣ ይረዳኛል
እስከ መጨረሻም ይመራኛል።
በመስቀል . . .።
፬፡ በዚህ ዓለም ስኖር አምላኬ ሆይ
እስከ መጨረሻ ከኔ ጋር ቆይ።
መከራ ጭንቀት ሲመጣ ስደት
ፍጹም አይለየኝም ካንተ ሕይወት።
በመስቀል . . .።
