Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 232 ደካማ መንገደኛ ነኝ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 232 ደካማ መንገደኛ ነኝ የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ ደካማ መንገደኛ ነኝ።
አንተ ግን ኃያል አምላክ፥
በጉዞዬ አንተ ምራኝ።
በብርቱ እጅህ ያዘኝ፥
ያንን ሰማያዊ ኅብስት
መግበኝ እንዳይርበኝ፤
መግበኝ እንዳይርበኝ።
፪፡ ከኃጢአት የሚያነፃኝን
የሕይወትን ምንጭ አፍልቅ።
በእሳት በደመና ዐምድ፥
መንገዴን ሁሉ ምራኝ።
ኃያል አዳኝ፥ ኃያል አዳኝ፥
ጋሻና ብርታት ሁነኝ፤
ጋሻና ብርታት ሁነኝ።
፫፡ ፍርሃትና ጥርጥርን
ፍጹም ከኔ አርቀህ፥
አዲሷ ኢየሩሳሌም
በሰላምህ አድርሰኝ።
ለዘላለም፥ ለዘላለም፥
እንድወድስህ አብቃኝ፤
እንድወድስህ አብቅኝ።

Exit mobile version