Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 228 የሱስ ሆይ ተቀበለኝ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 228 የሱስ ሆይ ተቀበለኝ የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ የሱስ ሆይ ተቀበለኝ
እኔ ወደ አንተ ስመጣ።
በመንፈስህ ጠብቀኝ
ከመለየት ከአንተ ጌታ
በየዕለቱ በየሰዓቱ
በደምህ እኔን አንፃኝ።
በምሕረትህ አቅርበኝ
በታላቅ ፍቅርህ ውስጥ ሰውረኝ።
፪፡ በዚህ ዓለም እስካለሁ
የሱስ ሆይ ምራኝ ባካሄዴ።
ባንተ ከተመራሁኝ
አይሳተኝም ከቶ መንገዴ።
በየዕለቱ . . .።
፫፡ ፍቅሬ እንዲጸናልኝ
በቅዱስ ቃልህ እኔን ምራኝ።
እሰማይ ስታደርሰኝ
እንዳመሰግንህ አምላኬ።
በየዕለቱ . . .።

Exit mobile version