Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 221 ጌታ የሱስ የዓለም መድኅን የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ጌታ የሱስ የዓለም መድኅን
የነገሥታት ንጉሥ
ባለ ጸጋ ሆነህ ሳለህ
ስለኔ ደኸየህ።
፪፡ ሥጋ ለባሽ ደካማ ነኝ
ጌታ ሆይ ና አጽናኝ።
ይህ ዓለም እንዳይደልለኝ
በቀኝ እጅህ ያዘኝ።
፫፡ ስለ እኔ የተቀበልከው
የመስቀል መከራ
አንደበቴን ያናግረው
ዓይኖቼንም ያብራ።
፬፡ በደምህ ነው የዋጀኸኝ
ፍጹም ገንዘብህ ነኝ።
ልቤን ሙላው በመንፈስህ
እንዳላሳዝንህ።
፭፡ አምላኬ ሆይ እኔን ጠብቅ
ወዳንተ እስክነጠቅ።
ይሁዳን ሆኜ እንዳላፍር
ና እምነቴን መርምር።
፮፡ ምስጋናህን እንዳልቀንስ
ከንፈሮቼን ዳስስ
ና ግባ በውስጤ ንገሥ
ልቦናዬን ቀድስ።