Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 209 አምላክ ሆይ አንተ ጠብቀኝ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 209 አምላክ ሆይ አንተ ጠብቀኝ የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ አምላክ ሆይ አንተ ጠብቀኝ
በቀናው መንገድ ምራኝ
ጨለማውን መንገድ አብራልኝ
ሕግህን እንድጠብቅ።
ኃጢአቴ ይሰማኛል
ሸክሙም በጣም ከብዶኛል።
በደሌን ደምስሰህ አንፃኝ
አምላኬ ሆይ ይቅታ ስጠኝ።
፪፡ ቸር ጌታ ሆይ አትተወኝ
አንተ ራስህ ጠብቀኝ፡
ታላቅ ፍቅርህም አይለየኝ
ልመናዬን ስማልኝ።
በሰማይና በምድር
ሁሉን የምትችል ነህ
በመንፈስ ቅዱስ አበርታኝ
ኃጢአቴን ደምስስልኝ።
፫፡ እንዳልካቸው ሐዋርያትን
ሂዱና አስተምሩ
መጣሁ ለመስማት ቃልህን
አእምሮዬን ክፈትልኝ።
ልቤን አንጽተህ ኑርበት
ጠላቴ እንዲርቅልኝ
ከክፉ ሁሉ አድነኝ
ጸሎቴን ስማ አሜን።

Exit mobile version