Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 197 የአምላኬን ውለታ ሁሉ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 197 የአምላኬን ውለታ ሁሉ የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ የአምላኬን ውለታ ሁሉ
ልቆጥረው ያቅተኛል፤
ከላይ እንደወረደው ጠሉ
በሁሉ ተረፍርፎአል።
የአምላኬን ውለታ ሁሉ
ልቆጥረው ያቅተኛል።
፪፡ ሳይሰየም ሳይመዘን ይቀራል
የፍቅሩ የጸጋውም ብዛት።
በጨለማ ውስጥ ግን ያበራል፤
በሌትም ይሰጣል ንጋት።
ሳይሰየም ሳይመዘን ይቀራል፤
የፍቅሩ የጸጋውም ብዛት።
፫፡ ልመዝነው ከቶ ባይቻለኝ፥
ይልቅ ላመሰግነው ነኝ።
የውለታው ትሩፋት ካለኝ፥
የፍቅሩ ብርታት ታወቀኝ።
ልመዝነው ከቶ ባይቻለኝ፥
ይልቅ ላመሰግነው ነኝ።

Exit mobile version