Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 197 የአምላኬን ውለታ ሁሉ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የአምላኬን ውለታ ሁሉ
ልቆጥረው ያቅተኛል፤
ከላይ እንደወረደው ጠሉ
በሁሉ ተረፍርፎአል።
የአምላኬን ውለታ ሁሉ
ልቆጥረው ያቅተኛል።
፪፡ ሳይሰየም ሳይመዘን ይቀራል
የፍቅሩ የጸጋውም ብዛት።
በጨለማ ውስጥ ግን ያበራል፤
በሌትም ይሰጣል ንጋት።
ሳይሰየም ሳይመዘን ይቀራል፤
የፍቅሩ የጸጋውም ብዛት።
፫፡ ልመዝነው ከቶ ባይቻለኝ፥
ይልቅ ላመሰግነው ነኝ።
የውለታው ትሩፋት ካለኝ፥
የፍቅሩ ብርታት ታወቀኝ።
ልመዝነው ከቶ ባይቻለኝ፥
ይልቅ ላመሰግነው ነኝ።
