Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 167 የኢየሩሳሌም ልጆች የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የኢየሩሳሌም ልጆች
ለየሱስ ዘመሩለት፤
እኛም በያለንበት እንደነርሱ
እንዘምር።
ዘምሩ ስሙን አመስግኑ፤
ዘምሩ ስሙን አመስግኑ፤
ሆሣዕና፥ ሆሣዕና፥ ሆሣዕና
ለዳዊት ልጅ።
፪፡ ንጉሥ ዳዊትም ያለው
ትንቢቱ ተፈጸመ፤
ከሕፃናት አፍ ደግሞ ምስጋናን
አዘጋጀህ።
ዘምሩ ስሙን . . .።
፫፧ ፍጥረት ሁሉ ተነሡ
ባንድነት ዘምሩለት።
እስከ ሰማይ እስኪደርስ
ድምፃችሁን ከፍ አድርጉ።
ዘምሩ ስሙን . . .።
