Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 157 ለሰርግ በክብር ሲጠራ የዘፈን ግጥሞች
፩፡ ለሰርግ በክብር ሲጠራ
ከሐዋርያቱ ጋራ።
ጌታም ሄደ በደስታ
ወደዚያው ወደ ሰርጉ ቤት።
መድኃኒታችን ኢየሱስ
እርሱ ነው የክብር ንጉሥ።
፪፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ
የቃል ኪዳን ሕግ ወዳጅ።
ጥሩውን ውኃ ለውጦ
አደረገው የወይን ጠጅ።
ከሰማይ የመጣልን
እርሱ ነው የአምላክ ልጅ።
፫፡ ቀምሶ አደነቀ በጣም
የተከበረው ካህን።
ለምን አቆየህ እስከ አሁን
ይህን ያማረውን ወይን?
በጣም የተሻለ ነበር
አስቀድመህ ብትሰጠን።
፬፡ የቃል ኪዳንንም ሥርዓት
ጌታ በቃሉ አጸናው።
እነዚህን ሁለቱ ሰዎች
ከእንግዲህ አንድ አካል ናቸው።
እስከ ዕለተ ሞታቸው
ማንም ሰው አይለያቸው።
፭፡ የዚህን ቃል ኪዳን ሥርዓት
የሚያፈርስ ሰው በኃይል።
በአምላካችን ፊት ቀርቦ
ጽኑ ፍርድን ይቀበላል።
በሰይጣንም እጅ ተይዞ
ይወርዳል ወደ ሲኦል።