Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982
መዝሙር 148 የጌታችን የየሱስ ሞት የዘፈን ግጥሞች
፩፡ የጌታችን የየሱስ ሞት
ለነፍሳችን ሆነ ሕይወት።
ጸጋና እውነት ሰላምም
አግኝተናል በርሱ ሕማም።
፪፡ ደሙን ስለ አፈሰሰ
ዕዳችን ተደመሰሰ።
በፍቅሩ ስለ ወደደን
ከአምላክ ጋር አስታረቀን።
፫፡ ጌታችንን እንመነው
ጸጋውን እንቀበለው።
መንፈስ ቅዱስን ሰጥቶናል
ቁርባኑንም ሠርቶልናል።
፬፡ ቅዱስ ሥጋውን ያበላናል፤
ቅዱስ ደሙን ያጠጣናል።
እንዲሆን ለሕይወታችን
እንውሰደው በልባችን።
፭፡ ይህ ሰማያዊ መና ነው
ይህ የዘላለም ሕይወት ነው።
ያን ኅብስት ስንቀበልም፥
ዘላለም አያልቅብንም።