Site icon Treasure Hymns – Amharic

መዝሙር 130 ቃልህን ኦ ቅዱስ ጌታ የዘፈን ግጥሞች

Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus vertion 1982

መዝሙር 130 ቃልህን ኦ ቅዱስ ጌታ የዘፈን ግጥሞች

 

፩፡ ቃልህን ኦ ቅዱስ ጌታ፥
ልንሰማ ሰብስበን፥
በልባችን እንዳዝመራ፥
ሊዘንብልን ባርከን።
መንፈስ ቅዱስን ስጠነ፥
ጸጋህንም ግለጥልን፥
የርበናል አቅምሰነ፥
ኦ ጌታችን ቃልህን።
፪፡ ቃልህንም ስትሰጠን፥
ልንጠብቀው እርዳን፥
ብርሃንህንም አብራልን፥
አሳየን መንገድህን።
ካለማመን ጠብከን፥
ከድንዛዜም አድነነ፥
በጸጋህም አሳድገን፥
በሕያው ቃልህ ምራን።
፫፡ በከንቱ ዘመናችንን፥
እንዳናሳልፈው እርዳን፥
ጸጋህን እንዳናባክን፥
አምላክ ሆይ አሳስበን።
ቃልህንም ስትነግረን፥
እንድንሰማው እርዳን፥
ልባችንንም አቅናልን፥
ልንታዘዝህ አብቃን።

Exit mobile version