መዝሙር 566 የመልአኩን ድምፅ ስሙ የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ የመልአኩን ድምፅ ስሙ
ምስጋና ለሕፃኑ
ምሕረት ሰላም ሰጠን
እኛም ካምላክ ታረቅን
ደስ ብሎአችሁ ተነሱ
ንጉሡን ተከተሉ
ከመልአክት ሠራዊት ጋር
ልደቱን እናክብር።
ኦ ቤትልሔም ውድ ቤትልሔም
ደስ ይበልሽ ዛሬ
ሆሳእና በአርያም ሕፃኑን እናንግሥ
መላእክትም ሕፃኑን ከበው
ምስጋና አቀረቡ
በሰማይ በምድር ለእርሱ
እልልታ አቅርቡ።
፪፡ ክርስቶስን እናክብር
ክርስቶስ የዘልዓለሙን
ነገዶች ሁላችሁ ኑ
ትሕትናን ተቀበሉ
በሥጋ ተገለጠ
ዘልዓለማዊ አምላክ
ከኛ ጋር ለመኖር
የሱስ የኛ አማኑኤል
ኦ ቤትልሔም . . .።
፫፡ ልዑሉን ኑና አንግሡ
ቅዱስ ቅዱስም በሉ
ሕይወት ብርሃንም ሰጠን
ምሕረቱንም አደለን
ክብሩን አጎናጸፈን
ሊያድነን ተወለደ
በኛ ፈንታ እርሱ ሞተ
ልጆቹም አደረገን
ኦ ቤትልሔም . . .።