መዝሙር 542 ክርስቶስ በመስቀሉ ላይ ሲሞትልን የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ ክርስቶስ በመስቀሉ ላይ ሲሞትልን
ኃጢአታችንን አርቆታል።
ባዳም አለመታዘዝ የመጣብን
ሁሉ በእርሱ ተወግዶአል።
ምንም ኃጢአት ሳይኖበት
ቅዱሱ የሞት ሥቃይ ቀምሶአል።
፪፡ ኃጢአታችን እንደ ቅርምዝ ቢሆን
እንደ በረዶ ይነጻልናል።
የሱስ በመስቀል ላይ ስለ ሞተልን
ጽድቅና ሕይወት ተገኝቶልናል።
የርሱን ሥቃይ በእምነት ስናይ
ከመቅሠፍት ከሞትም ያድነናል።
፫፡ የየሱስ ክርስቶስን ደም የሚንቁ
ኵነኔን ሳይፈሩ፥ በዚህ ሕይወት
ጸጋውንና ምሕረቱን የማያውቁ
ማን ያድናቸዋል ከሞት ጥፋት
የናቁትን ቸሩን መድኅን፥
በፍርድ ዕለት ያዩታል በፍርሃት።
፬፡ ኦ ጌታ የሱስ በቅዱ ሕማምህ
ኃጢአተኞችን አድነሃል።
ለኛ እረፍት ልትሰጥ በድካምህ
በደላችንን ተሸክመሃል።
ሁላችንን ልታድነን፥
በቅዱስ ደምህም ገዝተኸናል።
፭፡ አንተ በጎልጎታ ላይ የሞትህልን
የማዳንህን ጸጋ ግለጥልን።
ኦ የሱስ ክርስቶስ እንድናምንህ እርዳን፥
እኛም በመስቀልህ ኃይል እንዳን።
መስቀልህም ለዘላለም
ተስፋና ሕይወት ለእኛ ይስጠን።