መዝሙር 252 አመስግኑት የዘፈን ግጥሞች
Sibhat LeAmlak The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus. vertsion 2009
፩፡ አመስግኑት
አመስግኑት እግዚአብሔርን፥
ሃሌ ሉያ
አመስግኑት እግዚአብሔርን።
ለታላቁ
ለታላቁ ሕያው አምላክ፥
ልባችንን
ልባችንን እናስገዛው።
፪፡ አባታችን
አባታችን ልዑል አምላክ፥
መጠጊያችን
መጠጊያችን ነህ አምባችን።
ሥራችንን
ሥራችንን ሰርተኸዋል፥
ሃሌ ሉያ
ሃሌ ሉያ ክብር እንስጥህ።
፪፡ ስብሐት እንስጥ
ስብሐት እንስጥ ለጌታችን፥
ለጌታችን
ላምላካችን ለእግዚአብሔር።
ሥራችንን
ሥራችንን ሠርቶልናል፥
ሃሌ ሉያ
ሃሌ ሉያ እናክብረው።
፫፡ ዕልል በሉ
ዕልል በሉ አመስግኑት፥
እግዚአብሔርን።
እግዚአብሔርን ስሙን ጥሩ።
ደስ ይበለን
ደስ ይበለን እናመስግን፥
አምላካችን
አምላካችን ከኛ ጋራ ነው።